Lyrics
ባይሆን ኖሮ እግዚአብሔር ከኔ ጋር
ባይጋርደኝ ቅጥርን ባይቀጥር
ባይጋርደኝ ቅጥርን ባይቀጥር
ጠላቶቼ በቁጣቸው ብዛት
ህያው ሳለሁ በዋጡኝም ነበር
ህያው ሳለሁ በዋጡኝም ነበር
ግን እግዚአብሔር ምህረትን አበዛ
አሻገረኝ መንገድ አበጀና
አሻገረኝ መንገድ አበጀና
ይኸው ዛሬ በህይወት ቆሚያለሁ
በብዙ ድል በብዙ ምስጋና
በብዙ ድል በብዙ ምስጋና
ተጠነቀቀልኝ ጌታዬ ተጠነቀቀልኝ
ተጠነቀቀልኝ አምላኬ ተጠነቀቀልኝ
ተጠነቀቀልኝ አምላኬ ተጠነቀቀልኝ
ከጃቸው ሚያስጥል እንደሌለ እጅግ የበረቱ መሰሉ
አላስተዋሉትም ነበረ ከኔ ጋር ያለውን እረኛ
ድካም ከቶ እንደማያውቀው እኔን ለማዳን እንደማይተኛ
ስላለ ግን ጌታ ከጎኔ ስላል እርሱ ካጠገቤ
በጠላቴ ፉከራ ዛቻ ስጋት አይገባውም ይህ ልቤ
ተማምኜ በርሱ ተማምኜ በትከሻው መሃል አድራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ሰላም ነው ሁሉ ሰላም ነዉ
ጌታ ነው ከጎኔ ያለዉ
ደህና ነው ሁሉ ደህና ነዉ
ጌታ ነው በቤቴ ያለዉ
የላባ ቀንበር ቢከብደበት በቸገር ቢጠማ ቢከፋ
አመልጣለሁ ብሎ ቢያስብም ማልዶ ቢኮበልል ቢጠፋ
ተከታተለዉ ደረሰበት በቁጣው ሊያጠፋውም ዝቶ
የወደደውንም እንዲያደርግ በእጁ በሃይሉ ተመክቶ
የያቆብ አምላክ ቀደመ ለላባ በህልም ነገረው
እንክዋን ልትጎዳ ልታጠፋው በክፉ ቃል አትናገረው
በማስጠንቀቂያ ቃል ገስጾ ሃሳብ እቅዱን አፈረሰ
ያሳዳጁን ዛቻ ላልሰማው ለባሪያው ለያቆብ ደረሰ
ሰላም ነው ሁሉ ሰላም ነዉ
ጌታ ነው ከጎኔ ያለዉ
ደህና ነው ሁሉ ደህና ነዉ
ጌታ ነው በቤቴ ያለዉ
ባይሆን ኖሮ እግዚአብሔር ከኔ ጋር
ባይጋርደኝ ቅጥርን ባይቀጥር
ባይጋርደኝ ቅጥርን ባይቀጥር
ጠላቶቼ በቁጣቸው ብዛት
ህያው ሳለሁ በዋጡኝም ነበር
ህያው ሳለሁ በዋጡኝም ነበር
ግን እግዚአብሔር ምህረትን አበዛ
አሻገረኝ መንገድ አበጀና
አሻገረኝ መንገድ አበጀና
ይኸው ዛሬ በህይወት ቆሚያለሁ
በብዙ ድል በብዙ ምስጋና
በብዙ ድል በብዙ ምስጋና
ተጠነቀቀልኝ ጌታዬ ተጠነቀቀልኝ
ተጠነቀቀልኝ አምላኬ ተጠነቀቀልኝ
ተጠነቀቀልኝ አምላኬ ተጠነቀቀልኝ
እግዚአብሔር ብርሃኔ ነው ለኔ ጨለማው መንገዴን እንዳይዘጋ
ፍርሃት ስጋት ሁሉ ቀረ በልጁ ወደርሱ ስጠጋ
ተሰነካክዬ እንዳልቀር ህይወቴም እንዳትሆን ከንቱ
እንዳልሆንበት መሳለቂያ ገነነልኝ ለኔስ ምህረቱ
ስላለ ግን ጌታ ከጎኔ ስላል እርሱ ካጠገቤ
በጠላቴ ፉከራ ዛቻ ስጋት አይገባውም ይህ ልቤ
ተማምኜ በርሱ ተማምኜ በትከሻው መሃል አድራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
ዘላለም በክንፎቹ ጥላ በሰላም በደስታ ኖራለሁ
Lyrics powered by www.musixmatch.com