Lyrics
በለሷን ፍሬዋን የጠበቀ
ይበላል ትግስቱ ያላለቀ
ጌታውን የጠበቀ ሰው
ስፍሪዬን አለቅም ያለው
እሱ ሰው ከበረ አሄ
ጌታን ያከበረ
እሱ ሰው ከበረ አሄ
ጌታን ያከበረ
ስሞዖን ትጉህ ሰው ፃድቅ ሰው ነበረ
አያለው ቅዱሱን እያለ የኖረ
ሲጠብቅ ቆይቶ ህፃኑን ሲያየው
እጆቹን አንስቶ እንደዚህ አለው
ለህዝቦች ሁሉ መድኃኒት መድኃኒት
የሆነውን እሱን ስላየሁት ስላየሁት
መኖር አልሻም ውሰደኝ በቃ ውሰደኝ በቃ
በፅድቅ የኖርኩት እሱን ጥበቃ ጌታን ጥበቃ
ለኔ ስኬት ለኔ ስኬት
ለኔ ስኬት ልጁን ማየት
ለኔ ከፍታ ለኔ ከፍታ
ለኔ ከፍታ ፊትህ ነው ጌታ
ያርስ የለ ወይ በበጋ ልቡን ጥሎ
ገበሬው አምኖ ይዘንባል ብሎ
በደረቅ መሬት አምኖ ያረሰ
በክረምት እርሻው እረሰረሰ
እኔው እጠብቅሃለው
መውደዴን በዚ አሳይሃለው
አንድ ቀን ዓለም እያየህ
ልትወስደኝ ትመጣልኛለህ
እስክትመጣ እስክትመለስ
እጠብቅሃለው ውዴ ኢየሱስ
ጠነከረብኝ ፍቅርህ በረታ
በቶሎ ናልኝ የህይወቴ ጌታ
በለሷን ፍሬዋን የጠበቀ
ይበላል ትግስቱ ያላለቀ
ጌታውን የጠበቀ ሰው
ስፍሪዬን አለቅም ያለው
እሱ ሰው ከበረ አሄ
ጌታን ያከበረ
እሱ ሰው ከበረ አሄ
ጌታን ያከበረ
ፍጻሜው ክብር ነው አንተን መጠበቄ
መብራቴን አብርቼ ወገቤን ታጥቄ
እጠብቅሃለው እስክትመለስ
ሙሽራው አዳኜ ጌታዬ ኢየሱስ
ፊትህን እንዳይ ተርቤ የለ ወይ እርቦኝ የለ ወይ
ለጥቂቶች መዳን ብትዘገይ ብትዘገይ
ጨመረብኝ ፍቅርህ በየዕለቱ በየዕለቱ
ተናፍቀሃል ኢየሱስ የናዝሬቱ የናዝሬቱ
እስክትመጣ እስክትመለስ
እጠብቅሃለው ውዴ ኢየሱስ
ጠነከረብኝ ፍቅርህ በረታ
በቶሎ ናልኝ የህይወቴ ጌታ
Writer(s): Samuel Alemu, Bereket Tesfaye
Lyrics powered by www.musixmatch.com